👉የተከበርከው የትግራይ ህዝብ ሆይ የስግብግቡን ጁንታ ግብአተ መሬት ለመፈፀም በመጨረስ ላይ እንገኛለን፤ 

👉ጁንታው ቡድን በሁሉም አቅጣጫ ተከቧል፤ መውጫና መግቢያ አጥቶ ታፍኖ የሞት ጣር ላይ  ይገኛል፤ 

👉ባሁኑ ሰአት ስግብግቡ ጁንታው አመራር ለመስጠት በማይችልበት ደረጃ ደርሶ ይገኛል፤ ልጆችህ ያለ ምግብ እና ውሃ የሞት እራት እየሆኑ ነው ስለዚህ ልጆችህ ሂወታቸውን እንዳይሰጡ በፍጥነት አድን፤ 

👉የልጆችህ ሞት የጁንታውን እድሜ ለሰአታት ወይም ለቀናት ከማራዘም ውጪ ምንም ትርጉም የለውም፤ 

👉ሰው ለሃገር እና አለማ እንጂ ለጥፋት ቡድን ብሎ ሊሞትና አካሉ ሊጎድል አይገባም፤ 

👉ከትግራይ ህዝብ በላይ የጦርነት አስከፊነት የሚያውቅ የለም፤ ጁንታው ቡድን ለራሱ አይሞትም አካሉም አይጎድልም ስለዚህ የልጆችህ ደም ለጁንታው ቁማር መጫወቻ መሆን የለበትም፤ 

  👉 የልጆችህን ውድ ህይወወት ለማትረፍና ከአንበጣ የቀረውን እህልህን ወደ መሰብሰብ  እንድትመለስ ተጋግዘን ጁንታውን ቡድን ቶሎ ልንጨርሰው ይገባል ብዬ ጥሪዬን አቀርባለሁ፤ 

👉የተከበርከው የትግራይ ህዝብ ስግብግቡን ጁንታ ቶሎ መተን ወደ ልማታችን ልንመለስ ይገባል ስለዚህ የወጣት ልጆችህን ህይወት ቶሎ አድን፤ እያደረከው እንዳለሀውም መከላከያ ሰራዊትን አግዝ፤ 

👉በመስዋእትነት የገነባሀትን ኢትዮጵያ አሁንም በማዳን ታሪክህን  እንድታድስ ውድ አገርህ ጥሪ አድርጋልሃለች፤ 

👉በተለያየ የአመራር እርከን ያላችሁ ሲቪል መሪዎች ያለን ተቃርኖ በህወሓት ተሰግስገው ካሉ ጥቂት ሰዎች ጋር ብቻ ስለሆነ ራሳችሁን ከዚህ ጁንታ እንድታርቁ ጥሪ ቀርቦላችኋል፤ 

👉 መላው የትግራይ የፀጥታ አባላት በሙሉ ባለፉት ጥቂት ቀናት የገጠማችሁን አይታችኋል የስርአቱ ተጠቃሚዎች ወደ ሞት እያሰገቧችሁ ነው፤ እነሱ እየበሉ እየጠጡ እየተኙ እናንተ ግን በባዶ ሆዳችሁ የጥይት እራት እየሆናችሁ ነው፤ 

👉ጁንታው ቡድን አይደለም ደማቸውን ለመስጠት ሂወታቸውን ለመገበር ይቅርና የተኩስ ድምፅ ለመስማት እንኳ አይፈልጉም፤ ታድያ ለየትኛው አለማ ነው ወጣትነታችሁ በከንቱ የምታጠፉት፣ ለምን ትግራይን የወላድ ድሃ ታደርጓታላችሁ፣ ለምንስ ጉልበታችሁን ልማት ላይ አታውሉትም፣ 

👉ለዚህ ቀናት የቀሩት ጁንታ ቡድን ብላችሁ ህይወታችሁን ልትገብሩም ሆነ ደማችሁን ልታፈሱ በፍፁም ኣይገባም፤ 

👉 እጃቹህ ለመከላከያ በመስጠት አገራችሁ የሰጠቻችሁን እድል ሳያመልጣችሁ በሁለት ሶስት ቀናት ራሳችሁን አድኑ፤ 

ኢትዮጵያ በእውነተኛ ልጆችዋ ታሸንፋለች!

Please follow and like us:

By Eyasu Esayas

Entrepreneur, Writer, Business advocate and Teacher. Nice to have every soul on board. Eyasu do adore the HUMAN Nature. Join the Wonderful Team.

Leave a Reply

RSS
Follow by Email
Twitter
YouTube
Pinterest
LinkedIn
LinkedIn
Share
Instagram
Telegram
WhatsApp