ሠራዊታችን ሀገርን ከጥፋት የማዳን ተልዕኮውን በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደሚያጠናቅቅ የመከላከያ ኢንዶክትሪኔሽን ዋና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሜጀር ጄነራል መሀመድ ተሰማ አስታውቀዋል።

ሜ/ጀ መሀመድ ተሰማ የኢትዮጵያን ዕድገት የማይፈልጉ ታሪካዊ ጠላቶች የህዳሴ ግድባችንን እንዳያደናቅፉ የሀገራችን የፀጥታ ሀይሎች በተጠንቀቅ በቆሙበት ባሁኑ ሰዓት፣ የናት ጡት ነካሾች ሀገራችንን በመድፈር ውጊያ ከፍተውብናል ብለዋል።

ይህ ጦርነት ሀገርን ለውጭ አሳልፎ የሚሰጥና ፅንፈኛው ሀይል የስልጣን ጥማቱን ለማርካት የገባበት መሆኑንም ተናግረዋል።

በአሁኑ ሰዓት ይህንን ውጊያ ለመመከት መላው የፀጥታ ለይሎች እየተዋጉ ወንጀለኞችን ወደ ህግ ለማቅረብ ፍልሚያ ላይ እንደሚገኙ አስረድተዋል።

ዋና ዳይሬክተሩ እንደተናገሩት፣ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከዳር እስከዳር ተነሳስቶ የተከፈተብንን ጦርነት ለመመከት ተሳትፎውን በተለያየ መንገድ እየገለፀ ይገኛል።

ሠራዊታችን ፅንፈኛውን ሀይል በአጭር ጊዜ በቁጥጥር ስር በማዋልና ለህግ በማቅረብ የአካባቢው ሕዝብ ከነበረበት ጭቆና ነፃ እንደሚወጣ ሜ/ጀ መሀመድ አረጋግጠዋል ሲል የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት በማህበራዊ ገፁ አስታውቋል።

Please follow and like us:

By Eyasu Esayas

Entrepreneur, Writer, Business advocate and Teacher. Nice to have every soul on board. Eyasu do adore the HUMAN Nature. Join the Wonderful Team.

Leave a Reply

RSS
Follow by Email
Twitter
YouTube
Pinterest
LinkedIn
LinkedIn
Share
Instagram
Telegram
WhatsApp