የጉሌሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር አመራሮች፣ ሰራተኞች እና ነዋሪዎች ለመከላከያ ሰራዊት የደም ልገሳ መርኃግብር አካሄዱ፡፡

የደም ልገሳ መርኃግብሩ መከላከያ ሰራዊት ሀገርን ለመጠበቅ እያደረገ ያለውን ተጋድሎ ለመደገፍ ነው ተብሏል፡፡

በመርኃግብሩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ተፈራ ሞላ ኢትዮጵያ የብልፅግና ጉዞ እያደረገች ባለችበት ወቅት ጽንፈኛ ህወሓት የፈጸመው አስነዋሪ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በመሆኑም ከሀገር አልፎ ለቀጠናዊ ሰላም ሚናው የጎላ ለሆነው መከላከያ ሰራዊት ከጎኑ ለመሆናችን ማሳያ እንዲሆን ደም ለግሰናል ብለዋል፡፡

በጉሌሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አባወይ ዮሐንስ በበኩላቸው፣ “ደሜ ለሰራዊቴ፤ ህይወቱን ለሰጠኝ ደሜን እሰጣለው” በሚል መሪ ሐሳብ በክፍለ ከተማው የተከናወነው ተግባር ሁል ጊዜ ከሰራዊቱ ጎን መሆናችንን ለመግለጽ ነው ብለዋል፡፡

የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች ከዚህ በኋላም በማንኛውም ሁኔታ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡

አስተያየታቸውን ለዋልታ የሰጡ ደም ለጋሾች ጽንፈኛው ህወሓት የፈፀመውን ተግባር በማውገዝ ከመንግስት ጎን እንደሚቆሙ አረጋግጠዋል፡፡

Please follow and like us:

By Eyasu Esayas

Entrepreneur, Writer, Business advocate and Teacher. Nice to have every soul on board. Eyasu do adore the HUMAN Nature. Join the Wonderful Team.

Leave a Reply

RSS
Follow by Email
Twitter
YouTube
Pinterest
LinkedIn
LinkedIn
Share
Instagram
Telegram
WhatsApp