አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ የኢትዮጵያ መረጋጋት ለቀጠናው ወሳኝ መሆኑን ገለፁ፡፡

ዋና ፀሀፊው ድርጅታቸው በኢትዮጵያ የተጀመረው ሪፎርም ከዳር እንዲደርስና የኢትዮጵያ ህዝብ ተጠቃሚ እንዲሆን ከሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ጋር እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡

ስለሆነም የሀገሪቷ ሰላም ለምስራቅ አፍሪካ አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡

ድርጅታቸው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመሆን በሀገሪቷ ሰላም እንዲወርድና ህዝቦቿም ብሩህ ተስፋ እንዲኖራቸው እንሰራለንም ነው ያሉት፡፡

በትግራይ ክልል የተፈጠረው የፀጥታ ችግር በአስቸኳይ እንዲፈታና ህዝቡ ሰላማዊ ህይወቱን እንዲቀጥል አሳስበዋል፡፡

Please follow and like us:

By Eyasu Esayas

Entrepreneur, Writer, Business advocate and Teacher. Nice to have every soul on board. Eyasu do adore the HUMAN Nature. Join the Wonderful Team.

Leave a Reply

RSS
Follow by Email
Twitter
YouTube
Pinterest
LinkedIn
LinkedIn
Share
Instagram
Telegram
WhatsApp