“ብዙ ሰው አልቅሷል፣ ህዝብ ተገድሏል..ሰው ነኝና አጥችያለሁ። ፍትህ እፈልጋለሁ ። ቀነሱብኝ” ይላል ጀግናው ሻለቃ አትሌት ሃይሌ ገ/ስላሴ።

ለመሆኑ ኢትዮጵያ ውስጥ መንግስት አለ? በኦሮሚያ ክልል የወደመው ንብረት የሰው ልጆች ሞት ብዙ ጥያቄ ያስነሳል።

ሰመኑን አንድ ጓደኛዬ ከአመታት በፊት ሊቢያ ውስጥ የታረዱትን ወንድሞችን አስታወሰኝ። በአለም ላይ ተበትነን፣ በሃገራችን መኖር እንድንችል የሚያደርጉ የውጭ ጠላት ፍርፋሪ ለመብላት:- በወገን ላይ ሰይፍ ያነሱ ይጠየቁልን።

የህዝባዊ ወያኔ ትግራይ ነፃ አውጭ የተባለው በህዝባችን ደምና እምባ ላይ ዳግም መቀለድ ዋጋ ያስከፍላል። ይህን ግፍ በእኛ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ለማምጣት፣ ሃገር ለማከፋፈል ቀን ከሌሊት የሚሰሩ ሸፍጠኞች በአስቸኳይ ለፍርድ ይቅረቡ።

እኛ የኢትዮጵያ ህዝብ በሃገራችን በሰላም ገብተን በሰላም እንድንወጣ ህግ ይከበር። እነዚህ እና ሌሎች ወሳኝ ጉዳዮች ላይ መንግስት አስቸኳይ መፍትሄ እንዲያገኝ። መንግስት የተቀመጠው ህግን ለማስከበር ነው። ዜጎች በአደባባይ እየታረዱ፣ የአሩሲ አካባቢ ገዥዎች ቆመው የሚሄዱበት ፍትህ የለም። ሁሉም ሰው ወንጀለኛን ወደ ፍርድ በማቅረብ የበኩሉን ድርሻ ከተወጣ፣ ሃገር ሰላም ትሆናለች።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር ።

ቸር ያሰማን።

By Eyasu Esayas

Entrepreneur, Writer, Business advocate and Teacher. Nice to have every soul on board. Eyasu do adore the HUMAN Nature. Join the Wonderful Team.

How is that?

Discover more from Essu Center

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading