በሰሜን ኢትዮጵያ በመከላከያ ሠራዊት እየተወሰደ ያለው እርምጃ ግልጽ፡ የተወሰነ እና ሊደረስበት የሚችል ዓላማ ያለው መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታወቁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባለፈው ማክሰኞ ሕወሓት ትግራይ ክልል በሚገኘው የሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት መሰንዘሩን ተከትሎ መከላከያ ሠራዊት እርምጃ መውሰድ መጀመሩን በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ አስታውቀዋል። 

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመግለጫቸው፣ “በፌዴራል መንግሥት በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል እየተወሰደ ያለው እርምጃ ግልጽ፣ የተገደበ እና ግቡን የሚመታ ዓላማ ያለው ነው፤ ይህም የሕግ የበላይነትን እና ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን ለማስከበር እንዲሁም የኢትዮጵያውያንን መብት በማስጠበቅ በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ሰላማቸው ተጠብቆ እንዲኖሩ ለማድረግ ነው።” ብለዋል። 

መንግሥት ከሕወሓት አመራሮች ጋር ያለውን ልዩነት በሰላማዊ መንገድ በውይይት እና በሽምግልና ለመፍታት ለበርካታ ወራት በትዕግሥት ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ይሁን እንጂ በወንጀለኛው የሕወሓት ቡድን ሁሉም የሰላም ጥረት ውድቅ ሆኗል ብለዋል። 

በመጨረሻም ሕወሓት በትግራይ በሚገኘው የሰሜን እዝ ላይ ጥቃት መፈፀሙን ገልጸዋል።

By Eyasu Esayas

Entrepreneur, Writer, Business advocate and Teacher. Nice to have every soul on board. Eyasu do adore the HUMAN Nature. Join the Wonderful Team.

How is that?

Discover more from Essu Center

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading