በዘመናት መካከል ጠብቆ ያኖረንን ፈጣሪ እግዚአብሔርን የሚያመልከው ዘማሪ ደረጀ ከበደ (ዶ/ር) ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ ደብዳቤ ጽፎ በአደባባይ አስነብቧል።

እርግጥ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ሁኔታ አሳሳብም ከመሆኑም በላይ አፋጣኝ መፍትሄ ካልተወሰደ እልቂት እያስከተለ ነው። ኦሮሚያ ክልል ተብሎ በሚጠራው ሰፊ የሃገራችን ክፍል የሰው ልጅ ነፍስ ዋጋ ካጣች ሰነባብቷል። በአደባባይ ላይ ሰው ተገድሎ ተሰቅሏል። ቤተክርስትያን ተቃጥሏል። የሰው ልጅ ከነ ነፍሱ በቤቱ ውስጥ ተቃጥሏል። እርጉዝ ሴት ሆዷ ውስጥ ካለው ልጇ ጋር በዘጠኝ ወር ጊዜዋ ታርዳለች።

መከራና ስቃይ የበዛበት የኢትዮጵያ ህዝብ አሁንም፣ ዛሬም አማራ ወይም ክርስትያን በመሆኑ ብቻ የሰው ልጅ በኦሮሚያ ክልል እየሞተ ነው።

መንግስት ለዚህ ሁሉ አደጋ ከውጭ ሃይል ጋር የሚሰሩ ቡድኖች ያሉትን እያሰረ መሆኑ ይታወቃል። የዘር ማጥፋት ወንጀል የሚፈጽሙትን ለማስቆም ያለው ቁርጠኝነት የሚደነቅ ብሆንም የህይወት አድን እና የታርካችን ከባው ውሳኔ የሚያስፈልግ መሆኑ ግልፅ ነው።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዶ/ር ደረጀ ከባደ በመራር ቃላቶች ለክቡር ዶ/ር አብይ አህመድ መልዕክት አስተላልፏል። ሙሉውን ተከታተሉ። (Video for Ethio- 360 Media )

By Eyasu Esayas

Entrepreneur, Writer, Business advocate and Teacher. Nice to have every soul on board. Eyasu do adore the HUMAN Nature. Join the Wonderful Team.

Say Something