የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ለምርጫ ቀን ቀጠሮ አሰናድቷል።

ኢትዮጵያ ውስጥ ምርጫ የማስፈጸም ብቸኛ አካል ፈደራል ብሄራዊ ምርጫ ኮምሽን ብቻ መሆኑ ይታወቃል። በህወሃት የሚመራው የትግራይ ብሔራዊ ክልል በሃገር ደረጃ የተራዘመውን ምርጫ ባለመቀበል ለምርጫ ሂደት እንደተዘጋጀ አስታውቋል ።

እንደ ትግራይ ክልል መግለጫ ጻጉሜ አምስት ላይ ምርጫ እንደምካሄድ አሳውቀዋል። ለዚህ የምርጫ አፈጻጸም የሚያስፈልገውን ግብአት በክልል ደረጃ እንደተሰናዳ አስታውቀዋል።

የፌደረሽን ምክር ቤት ከምርጫ ጋር በተያያዙ በምደረጉ እንቅስቃሴዎች ለትግራይ ክልል መንግስት ማስጠንቀቂያ መላኩ ይታወሳል። በአሁኑ ጊዜ ምን አይነት እርምጃ ሊወሰድ እንደምችል የታወቀ ነገር ባይኖርም ህግና ስርአትን ለማስከበር እንደምሄዱ በተደጋጋሚ አስታውቀዋል።

የትግራይ ክልል ማስታወቂያ ብሮና በአካባቢ ላይ የሚሰሩ ሚዲያ እንደገለጹት አለም አቀፍ የምርጫ ታዛብ ሳይቀር እንደተጋቡዙና ከ 70 በላይ ሃገሮችን ጭምር እንደጋበዙ እየተነገረ ነው።

(By: Eyasu Esayas)

Say Something