አንቶኒዮ ጉተሬዝ የኢትዮጵያ ሰላም ለቀጠናው ወሳኝ መሆኑን ገለፁ

Estimated read time 0 min read

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ የኢትዮጵያ መረጋጋት ለቀጠናው ወሳኝ መሆኑን ገለፁ፡፡

ዋና ፀሀፊው ድርጅታቸው በኢትዮጵያ የተጀመረው ሪፎርም ከዳር እንዲደርስና የኢትዮጵያ ህዝብ ተጠቃሚ እንዲሆን ከሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ጋር እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡

ስለሆነም የሀገሪቷ ሰላም ለምስራቅ አፍሪካ አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡

ድርጅታቸው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመሆን በሀገሪቷ ሰላም እንዲወርድና ህዝቦቿም ብሩህ ተስፋ እንዲኖራቸው እንሰራለንም ነው ያሉት፡፡

በትግራይ ክልል የተፈጠረው የፀጥታ ችግር በአስቸኳይ እንዲፈታና ህዝቡ ሰላማዊ ህይወቱን እንዲቀጥል አሳስበዋል፡፡

Eyasu Esayas https://canada3sponsor.com

Entrepreneur, Writer, Business advocate and Teacher.
Nice to have every soul on board.
Eyasu do adore the HUMAN Nature.
Join the Wonderful Team.

You May Also Like

More From Author

+ There are no comments

Add yours

Say Something