ስግብግቡና አረመኔው የመቐለ ጁንታ ለፍትህ ቀርቦ ተገቢውን ቅጣት ሳያገኝ ለአፍታም ቢሆን አናርፍም – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ስግብግቡና አረመኔው የመቐለ ጁንታ ለፍትህ ቀርቦ ተገቢውን ቅጣት ሳያገኝ ለአፍታም ቢሆን አናርፍም ብለዋል። 

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት ስግብግቡና አረመኔው የመቐለ ጁንታ በሰሜን ኮማንድ አባላት ያደረሰውን ኢ-ሰብአዊ ግድያ፣ ግፍ እና በደል መቸውንም አንረሳውም ነው ያሉት። 

የህግ የበላይነት የማረጋገጥ ስራው ሳይጠናቀቅ ከጁንታው ቡድን ጋር ድርድር እንደማይኖርም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ዳግም አረጋግጠዋል።

Say Something